Thursday 3 August 2017

ዕውቀትን በጋሻ የሚከላከል ትውልድ

By Derbe Tefera


ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ በታችኛው የትምህርት እርከንና በዩኒቨርሲቲዎቻችን አካባቢ የዕውቀት ድርቅ እየተከሰተ እንደሆነ ብዙዎች ይገምታሉ፡፡ በሃገራችን የትምህርት ታሪክ የንባብ ወኔና ፍቅር የነበራቸው ተማሪዎች ከንጉሱ ስርዓት ጋር ዳግም ላይመለሱ የጠፋ ይመስላል፡፡በ1960 እና 70ዎቹ የነበረው የተማረ ትዉልድ ከሚታወቅባቸዉ ነገሮች መካከል ለሃገር እድገት ፣ አንድነት ፣ ለፍትህ ፣እኩልነት ፣ ነፃነት መታገል እንድሁም ጠንካራ የንባብ ባህል እና ሌሎችም ይጠቀሳሉ፡፡ አሁን ላይ ግን በተቃራኒው በትምህርት ተቋማት አካባቢ መሃይምነት ሞቅ ያለ አቀባበል እየተደረገለት ነው፡፡ተማሪዎች ለትምህርት ያላቸው ቦታ እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡ኩረጃን እንደ ዘመናዊነት በመቁጠር አውቆ ማግኘት የሚለውን ብሂል እያጠፋን ነው፡፡ፈተና ይኮረጃል ፣ ለምረቃ የምርምር ስራ ይቀዳል ፣ የቀለም አባትና ልጅ እርስ በርስ መከባበር ቀርቷል፤ በትምህርት ዓለም ኩረጃ የለመደ ትውልድ በስራ ዘመኑ፥
❖የህዝብን ካዝና ላለመዝረፋ ፣
❖ፍትህ ላለማዛባቱ ፣
❖የመልካም አስተዳደር እንቅፋት ላለመሆኑ ፣
❖የሃገር ሸክም ፣
❖ግብረ-ገብነት የጎደለው ፣
❖የማህበረሰቡን ሰላም አደፍራሽ ፣
❖የነፃነት ካቴና ላለመሆኑ እና የችግሮች ሁሉ ምንጭ ላለመሆኑ ምን ዋስትና አለን፡፡

በመጨረሻም ሰራው አጋልጦት "ዳኛና ወራጅ ውሃ ከፊት ያገኘውን አይለቅም "እንደሚባለው ተይዞ ከታሰረና ለዓመታት ከተቀጣ ወጣት ሆኖ ገብቶ ከማረሚያ ቤት ሸበቶ አብቅሎ ይወጣና ከዘራ ይዞ በፀፀት ጎዳና ቀሪ ህይወቱን ይመራል፡፡የሚያሳዝነው ነገር ለራሱ ፣ ለቤተሰብ ፣ ለአደገበትና ላሳደገው ማህበረሰብ እንድሁም ለሃገር ምንም ሳይጠቅም የሞራል ልዕልናም ሳይኖረው ፤
የትም ውሎ ከቤት ፣
ኑሮ ኑሮ ከሞት
መቅረት አይቻልም እንደሚባለው እለተ ሞቱ መድረሱ ነው፡፡

ልክ ጥሬ ዕቃ እንደሌለው ፋብሪካ፥ ጭንቅላቱ የዕውቀት እርሾ የሌለው ባዶ (ለማለት ቢከብድም) ትውልድ መፈጠሩ አይቀርም እየተፈጠረም ነው፡፡/ጥቂቶችን አይመለከትም፡፡ ጅምላ ፈፍረጃ አይደለም፡፡/
ችግሩ ከምንም በላይ ያስፈራል፡፡ ለነገሩ ፦

✿አጥንት የሚወጉ የጤና ባለሙያዎች + ከልምድ አዋላጆች የማይሻሉ ፣
✿ስማቸውን መፃፍ የሚከብዳቸው ምሩቃን (የተጋነነ አይምሰላችሁ ያጋጠመኝ ነገር ነው
✿የሳይኮሎጅ ምሩቅ ሆነው ለማህበረሰቡ የምክር አገልግሎት መስጠት ሲገባቸው ራሳቸውን ከስነ-ልቦና ቀውስ ማውጣት ያልቻሉ፣
✿ ፍ/ቤቶች በደመነፍስና በልምድ ከህግ ዕውቀት ነፃ በሆነ ትውልድ ሲጥለቀለቁ ማየት ያላሰፈራ ከቶ ሌላ ምን ያሰፈራል፡፡

በብዙዎቻችን ዘንድ መማር ከኃላ ቀርነት ፣ ከድህነት እና ከድንቁርት መላቀቅ ሳይሆን መማረር ሲያልፍም በተቃራኒው እየታየ መጥቷል፡፡
አልፈልግም ድግሪ ፣
ይቅርብኝ ማስትሬት ፣
ስንዝሯ ይበቃል ፣

የሰበታ መሬት፡፡ እንደተባለው ወገኖቻችን ከዕውቀት ማዕድ ላይ ተነስተው በቢዝነስ ጎዳና ላይ መጓዝን ምርጫቸው እያደረጉ ነው፡፡ ሃገር በዕዉቀት ድርቅ ለመመታቷ ሌላ ምን ማረጋገጫ ይኖራል፡፡ በስራ ላይ ያለዉ የተማረዉ ሃይል ስራውን እየተወ መውጣት ከጀመረ እና ልመምድ በሌላቸው ከመንግስት የስራ ባቡር ለይ ተሳፍረው ቅርብ ወራጅ በሆኑት መተካት ከተጀመረ ቆየ፡፡ይህ ጉዳይ ከደመወዝ እና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች ጋር በቀጥታ ይገናኛል፡፡ ሰለዚህ መንግሰት የራሱን አሳይመንት ሊወጣ ግድ ይለዋል፡፡ በፊት የነበረው የተማረ ሰው ክብር ዛሬ ላይ የት ደረሰ?

በመማርህ ሁለት ጊዜ አትሰደብ፡፡ይህን ያልኩት ወድጀ አይደለም፥ አንድ ሰው እንድህ ሲል አጫወተኝ ፦ ስድብ እንኳን ተቀይሮ በፊት አንተ የምን ልጅ ይባል የነበረው አሁን አንተ የመንግስት ሰራተኛ እና አንተ የመምህር ልጅ በሚል ሊቀየር ነው ብሎ ቀለደ፡፡

ወገኖቸ አንተ የተማርክ መሐይም ከሚለው የሁለተኛው ስድብ ይሰውረን እላለሁ፡፡ዛረሬ ለላይ በመማርህ ትሰደባለህ ፣ ተምረህ ባለማወቅህ ግን የበለጠ ትሸማቀቃለህና ከንባብ አትመለስ፡፡ "The one who graduated yesterday & stop reading today is uneducated tomorrow" ይባላልና ትምህርት ማለቂያ ሰለሌለው እንድሁም የምታውቀውን ነገር "update" ማድረግ ሰላለብህ የመንግስት ሰራተኛ ከሆንክ ዋናውን እንጀራ ማግኘት ቢከብድህም ከ አ/አ ሰጋቱራ እንጀራ መስል የእንጀራ "High Copy" ራስህን እየጠበክ አንብብ፡፡ ሰጋቱራ ግን ሌላ ድርቀት ነውና ተከላከለው፡፡ የሆድ እና የዕውቀት ድርቀት ከያዘህ አገርህን መጥቀም አትቸችልም፡፡
እውቀትን ሳይሆን መሃይምነትን በጋሻ አእንከላከል፡፡ የቢዝነሱ ዓለምም ዕውቀትን ይፈልጋልና ሱቅ በደረቴ ሆነህም እንዳትቀር ዕውቀት ሊኖርህ ይገባል፡፡

ዘላቂዉ መፍትሄ ምን ይመስላችኃል??????

1 comment:

የፖለቲካ ባህላችን

አየሽ እዚህ አገር ከንቱ ፍረጃ አለ፤ አማኝ ሁሉ አክራሪ፤ ሙስሊሙ አሸባሪ፤ ጉራጌ ቋጣሪ፡፡ ትግሬ ሁሉ ወያኔ፤ ወጣቱ ወመኔ፡፡ አማራው ነፍጠኛ ፤ ደርግ ሁሉ ግፈኛ፡፡ ናቸው እያስባለ ፤ ቁልቁል የሚነዳን ጭ...