By Derbe Tefera
በሃገራችን ለዘመናት የፍትህ ስርዓቱን ሲፈታተኑት ከቆዩትና ዛሬም ማስወገድ ካልቻልናቸው ጉዳዮች/ተግዳሮቶች መካከል አንዱ ነው ***የሐሰት ምስክርነት***፤ይባስ ብሎ ከጊዜ ወደ ጊዜ በማህበረሰባችን ዘንድ እንደ ነውር መቆጠሩንም እየረሳን መጥተናል፡፡ ዓለም ለእምነታችን ባለን ጥንካሬ ማረጋገጫ የሰጠችን እና ሰለ እውነት ይሞታሉ የምንባል ህዝቦች እነሆ ዛሬ ላይ እሴቶቻችን እየጠፉ ስለ እውነት መኖርን በመተው በሐሰት ጎዳና መኳተን ከጀመርን ሰነበትን፡፡
በሐሰት ምሰክርነት መዘዝ የተነሳ ምንም ሳያጠፉ ፀጉራቸውን ተላጭተው ከርቸሌ የወረዱትንና ወንጀል ሰርተው ግን ነፃ ናችሁ ተብለው የሰላም አየር የሚተነፍሱትን ዜጎች ቁጥር እኛ ሰለማንደርስባቸው አሳይመንቱን ለፈጣሪ ሰጥተናል/ፍትህ ሚ/ር እንኳን አይችለውም/
ህሊናችን ካልገዛን በስተቀር ፍ/ቤቶች ምንም ያክል ጠንካራ ስርዓት ቢዘረጉ ችግሩን ማስቀረት አይችሉም፡፡
በፍትሃ ብሔር ስነ-ስርዓት ህግ ቁ 263 ላይ እንደተደነገገው ለምስክሮች አራት /4/ አይነት ጥያቄዎች ይቀርባሉ፡፡ እነዚህም ፦
1ኛ. ዋና ጥያቄ /Main examination/
2ኛ.መስቀለኛ ጥያቄ/ Cross examination/
3ኛ.ማጣሪያ ጥያቄ/Re-examination/
4ኛ.መሪ ጥያቄ/Leading question/ ናቸው፡፡ ምስክር ቃሉን ከመስጠቱ በፊት መሃላ ይፈፅማል አልያም የሚሰጠው ቃል እውነት መሆኑን ማረጋገጥ ይኖርበታል፡፡ መፍትሄ ግን ሲሆን አላየንም፡፡ አሰራር ሰለሆነም ተቃውሞ የለንም፡፡
ህጉ ይህን ቢልም በተግባር ግን በዝምድና ፣ የተለየ ጥቅም በመፈለግ ፣ በሃይል ጫና በመፍጠርና በሌሎች ምክንያቶች ሰው ህሊናውን እና ፈጣሪውን ክዶ በሐሰት ይምላል ፤ ይመሰክራል፡፡
የድርጊቱ ጉዳትም የትየለሌ ነው፡፡ "የአይጥ ምስክሯ ድንቢጥ" እንደሚባለው ሆነና ነገሩ ፍትህ ላይመለስ ከሃገራችን ሰማይ ራቀ፡፡ ፈጣሪም መታዘቡንና በኛ ማዘኑን ቀጠለ፡፡ እስከመቼ???
ለነገሩ ****Justice is sold at a high price*** ይሉ የለ ፈረንጆችስ፡፡
ኧረ ፍትህ እንደ ውሃ ጠማን ፥ ማነው ተጠያቂ? መንግስት? ህዝብ? ወይስ ሌላ አካል?
ለፍትህ ስርዓቱ በዕንቅርት ላይ ጆሮ ገድፍ የሆነው ፨የሐሰት ምስክርነት ፨በእስካሁኑ ይብቃ፡፡
ለህሊናችን እንገዛ!!!
በሌሎች የዳኝነት ችግሮች ላይ እመለሳለሁ፡፡
No comments:
Post a Comment