እንረስ ካላችሁ ተስማምተን እንረስ ፤
አይሆንም ካላችሁ ተውት ዳዋ ይልበስ፡፡
.
ወቅታዊ የአገራችን ሁኔታ እጅጉን አሳሳቢ ሆኗል፡፡ ኢትዮጵያ ከማትወጣበት የጥላቻ ፓለቲካ ባህር ውስጥ ገብታለች፡፡ የዘውግ ፌደራሊዝሙ የታሰበለትን አላማ ሊያሳካ አልቻለም፡፡ ይባስ ብሎ በእሳት ላይ ነዳጅ መጨመር ሆኗል፡፡ ሁሉም የአገሪቱ ዜጋ ኢትዮጵያን ማስቀደም ሲገባው ወደ ጎሳ ዘምቢል ራሱን እየጨመረ ነው፡፡ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወድህ እየተስተዋሉ ያሉ እንቅስቃሴዎች ኢትዮጰያ እንደ አገር የመቀጠል ተስፋ ላይኖራት ይችላል ያስብላሉ፡፡ በፅንፈኝነት ላይ የተመሰረተው ፓለቲካችን ፍሬ አፍርቶ ህዝብ ለህዝብ በጥላቻ መስኮት እንድተያይ አስችሏል፡፡ ይሄ ነገር ወደ እርስ በርስ እልቂት መውሰዱም ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡
በስልጣን ላይ ያሉት አካላትም ለአገራዊ ጥቅም ደንታ የላቸውም፡፡ <<ስለሞትን እንገዛለን>> በሚል አስተሳሰብ የስልጣን ጥማቸውን ለማርካት ህዝብን ከፋፍለው ለመግዛት የነደፋት የስልጣን ማቆያ ፕሮጀክት ትርፋማ ሆኗል፡፡ ዛሬ ላይ ከምክንያት ይልቅ ስሜት በአገራችን የፓለቲካ ሰማይ ነግሷል፡፡ በስሜት የሚመራ የፓለቲካ ማህበረሰብ ደግሞ እርስ በርሱ ይናከሳል፡፡ መንግስትን እንቃወማለን የሚሉ ግለሰቦች ፣ ቡድኖች እና የፓለቲካ ፓርቲዎች ሳይቀሩ በአመክንዮ ሳይሆን በደመነፍስ ሲንቀሳቀሱ ማየት እጅጉን ያበሳጫል፡፡ በስልጣን ላይ ያለው ወገን ከዙፋኑ ቢወርድ እንኳን <<ሌባ ሲሰርቅ ይስማማል ሲካፈል ይጣላል>> እንዲሉ ጤነኛ አስተሳሰብ የሌላቸው አንዳንድ የነፃነት ታጋይ ተብየዎች ተስማምተው አገር ያስተዳድራሉ ለማለት የሚያስችል ተጨባጭ እውነታ የለም፡፡ እነሱ ከመንግስት የሚለዩት ቤተ መንግስት ስላልገቡ ብቻ ነው ለማለት ያስደፍራል፡፡ ጉልቻ ቢላወጥ ወጥ አያጣፍጥም አይነት ነው ነገሩ፡፡
አንዳንድ ቡድኖችማ ጭራሹኑ ግልፅ የሆነ የፓለቲካ አቋም ብሎም ርዕዮተ ዓለም የላቸውም፡፡ ይቃወማሉ ግን ለምን ምን አላማ እንግበው እንደሆነ ግልፅ አይደለም፡፡ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው ማለት ይሄኔ ነው፡፡
ከሁሉም የበለጠውና አሳሳቢው ጉዳይ ግን የጥላቻ ፓለቲካችን መዘዝ ነው፡፡ በዚህ ከቀጠልን ማየት የማንፈልገው መጥፎ ነገር ይፈጠራል፡፡ በኦሪት ህግ የሚመራው የአገራችን ፓለቲካ ጥፋት አርግዟል፡፡ በመንግስት ሰፓንሰር የሚደረገው ይህ ጥላቻ አዘል አካሄድ አገር ያጠፋልና አስቸኳይ መፍትሔ ይሻል፡፡
ህዝብ ለህዝብ መተባበር ካልቻለ ሁሉም ነገር ቀሪ ነው፡፡ አገር ዳዋ ለበሰች ማለት ከዚህ የተለየ አይደለም፡፡ አገራዊ መግባባት እስካልተፈጠረ ድረስ የስርዓት ለውጥ ቢደረግ እንኳን ኢትዮጵያ ከፓለቲካ ደዌ አትድንም፡፡
.
በአመክንዮ የሚመራ ማህበረሰብ እንፍጠር!
አይሆንም ካላችሁ ተውት ዳዋ ይልበስ፡፡
.
ወቅታዊ የአገራችን ሁኔታ እጅጉን አሳሳቢ ሆኗል፡፡ ኢትዮጵያ ከማትወጣበት የጥላቻ ፓለቲካ ባህር ውስጥ ገብታለች፡፡ የዘውግ ፌደራሊዝሙ የታሰበለትን አላማ ሊያሳካ አልቻለም፡፡ ይባስ ብሎ በእሳት ላይ ነዳጅ መጨመር ሆኗል፡፡ ሁሉም የአገሪቱ ዜጋ ኢትዮጵያን ማስቀደም ሲገባው ወደ ጎሳ ዘምቢል ራሱን እየጨመረ ነው፡፡ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወድህ እየተስተዋሉ ያሉ እንቅስቃሴዎች ኢትዮጰያ እንደ አገር የመቀጠል ተስፋ ላይኖራት ይችላል ያስብላሉ፡፡ በፅንፈኝነት ላይ የተመሰረተው ፓለቲካችን ፍሬ አፍርቶ ህዝብ ለህዝብ በጥላቻ መስኮት እንድተያይ አስችሏል፡፡ ይሄ ነገር ወደ እርስ በርስ እልቂት መውሰዱም ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡
በስልጣን ላይ ያሉት አካላትም ለአገራዊ ጥቅም ደንታ የላቸውም፡፡ <<ስለሞትን እንገዛለን>> በሚል አስተሳሰብ የስልጣን ጥማቸውን ለማርካት ህዝብን ከፋፍለው ለመግዛት የነደፋት የስልጣን ማቆያ ፕሮጀክት ትርፋማ ሆኗል፡፡ ዛሬ ላይ ከምክንያት ይልቅ ስሜት በአገራችን የፓለቲካ ሰማይ ነግሷል፡፡ በስሜት የሚመራ የፓለቲካ ማህበረሰብ ደግሞ እርስ በርሱ ይናከሳል፡፡ መንግስትን እንቃወማለን የሚሉ ግለሰቦች ፣ ቡድኖች እና የፓለቲካ ፓርቲዎች ሳይቀሩ በአመክንዮ ሳይሆን በደመነፍስ ሲንቀሳቀሱ ማየት እጅጉን ያበሳጫል፡፡ በስልጣን ላይ ያለው ወገን ከዙፋኑ ቢወርድ እንኳን <<ሌባ ሲሰርቅ ይስማማል ሲካፈል ይጣላል>> እንዲሉ ጤነኛ አስተሳሰብ የሌላቸው አንዳንድ የነፃነት ታጋይ ተብየዎች ተስማምተው አገር ያስተዳድራሉ ለማለት የሚያስችል ተጨባጭ እውነታ የለም፡፡ እነሱ ከመንግስት የሚለዩት ቤተ መንግስት ስላልገቡ ብቻ ነው ለማለት ያስደፍራል፡፡ ጉልቻ ቢላወጥ ወጥ አያጣፍጥም አይነት ነው ነገሩ፡፡
አንዳንድ ቡድኖችማ ጭራሹኑ ግልፅ የሆነ የፓለቲካ አቋም ብሎም ርዕዮተ ዓለም የላቸውም፡፡ ይቃወማሉ ግን ለምን ምን አላማ እንግበው እንደሆነ ግልፅ አይደለም፡፡ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው ማለት ይሄኔ ነው፡፡
ከሁሉም የበለጠውና አሳሳቢው ጉዳይ ግን የጥላቻ ፓለቲካችን መዘዝ ነው፡፡ በዚህ ከቀጠልን ማየት የማንፈልገው መጥፎ ነገር ይፈጠራል፡፡ በኦሪት ህግ የሚመራው የአገራችን ፓለቲካ ጥፋት አርግዟል፡፡ በመንግስት ሰፓንሰር የሚደረገው ይህ ጥላቻ አዘል አካሄድ አገር ያጠፋልና አስቸኳይ መፍትሔ ይሻል፡፡
ህዝብ ለህዝብ መተባበር ካልቻለ ሁሉም ነገር ቀሪ ነው፡፡ አገር ዳዋ ለበሰች ማለት ከዚህ የተለየ አይደለም፡፡ አገራዊ መግባባት እስካልተፈጠረ ድረስ የስርዓት ለውጥ ቢደረግ እንኳን ኢትዮጵያ ከፓለቲካ ደዌ አትድንም፡፡
.
በአመክንዮ የሚመራ ማህበረሰብ እንፍጠር!
No comments:
Post a Comment